Episodios

  • የጥር 10 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    Jan 18 2026
    ግብፅ እና ሱዳን የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ሀሳብ አወደሱ፤የኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች የከተራ በዓልን በድምቀት እያከበሩ ነው፤ኡጋንዳ የኢንተርኔት አገልግሎት በከፊል መስራት ጀመረ፤ በኢራን ፀረ መንግሥት ተቃውሞዎች እስከ 18,000 የሚደርሱ ሰዎች ሳይገደሉ አልቀረም፤የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈፀመ
    Más Menos
    10 m
  • የጥር 9 ቀን፤ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
    Jan 17 2026
    የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአባይ ውሃ ባለድርሻነት ለአንዴና ለዘለቄታው እልባት እንዲያገኝ በሚል ግብጽ እና ኢትዮጵያን ዳግም ወደ ድርድር ለማስገባት አገራቸው አሜሪካ ቁርጠኛ መሆኗን አስታወቁ፡፡ የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራም የግብፁ ፕረዚደንት ዓብደልፋታሕ አልሲስን የጋዛ የሰለም ቦርድ አድርገው ማጨታቸውን ታውቋል።የ81 አመቱ የኡጋንዳ ፕረዚደንት ዩዌሪ ሙሰቨኒ ሐሙስ ዕለት በተካሄደም ምርጫ ማሸነፋቸውን የሐገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን ዛሬ ይፋ አደረገ። ሩስያ ሌሊቱን ለዛሬ አጥቢያ በዩክሬይን ግዛት በፈጸመችው ጥቃት አንድ የነዳጅ ማጣሪያ ተቋም ማውደሟን ናፍቶ-ጋዝ የተባለ የግል ኩባንያ አስታወቀ።
    Más Menos
    11 m
  • የጥር 8 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
    Jan 16 2026
    • ከሑመራ ዞን የተፈናቀሉ ሰዎች “ደሕንነታቸው ተጠብቆ በክብር፣ መረጃ ኖሯቸው እና በፈቃደኝነት” ወደ ቀያቸው መመለስ መጀመር አለበት የሚል አቋም አሜሪካ እንዳላት በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ተናገሩ። • በዩጋንዳ ትናንት ሐሙስ በተደረገው እና ዛሬ ውጤቱ ይፋ ይደረጋል ተብሎ በሚጠበቀው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በተቀሰቀሰ ተቃዉሞ በትንሹ አስር ሰዎች ተገደሉ። • አዲሱን የጋዛ የሽግግር አስተዳደር ስራ የሚቆጣጠር ዓለማቀፍ ተቆጣጣሪ ቦርድ ማቋቋማቸውን የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናላድ ትራምፕ አስታወቁ። • በኢትዮጵያ የፊልምና የመዝናኛ ዘርፍ እውቁ አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
    Más Menos
    12 m
  • የጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
    Jan 15 2026
    በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ስምንት ፓርቲዎች ሀገራዊ ምክክር በክልሉ እንዲካሄድ ለማገዝ ተስማሙ። ሐማስ በአሜሪካ ተነሳሽነት የተጀመረውን የተኩስ አቁም ስምምነት ሁለተኛ ክፍል አካል የሆነውን በፍልስጤም ይቋቋማል የተባለውን የባለሙያዎች ኮሚቴ እንደሚቀበለው አስታወቀ። የጀርመን የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪ ባለስልጣን የጀርመን አውሮፕላኖች በኢራን የአየር ክልል እንዳይጠቀሙ አሳሰበ። የአውሮፓ ሕብረት አባል ሐገራት ወታደሮቻቸውን የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ እጠቀልላታለሁ ወዳሏት ግሪንላንድ መላክ ጀመሩ።
    Más Menos
    10 m
  • የረቡዕ ጥር 6 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
    Jan 14 2026
    ጁባ፥ የኢትዮጵያ እና የደቡብ ሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ከፍተኛ ልዑካን ተወያዩ፣ ሞቃዲሾ፥ ሶማሊያ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጋር የነበራትን ስምምነት ሙሉ በሙሉ አቌረጠች፣ባማኮ፥ የነዳጅ እጥረት በማሊ በረራ እንዲሰረዝ አስገድዷል፣ ፓሪስ፥ ፈረንሳይ ግሪንላንድን በተመለከተ የትራምፕ አስተዳደር የሰጠውን ቀስተያየት በቀላሉ ዐታየውም፣ቴሕራን፥ የኢራን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰልፈኞችን በአፋጣኝ ሒደት እንደሚቀጣ ዛተ
    Más Menos
    9 m
  • የጥር 5 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
    Jan 13 2026
    • በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሁለት የቱርኪዬ ዜጎች እና አንድ ኢትዮጵያዊ "ባልታወቁ" ታጣቂዎች ተገደሉ። • ምዕራብ ወለጋ ዞን ውስጥ ለመስክ ስራ የወጡ የቴሌኮም ሰራተኞች በታጣቂዎች መታገታቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ። • የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የኢትዮጵያ ገዢ የብልጽግና ፓርቲ «አጀንዳ ቀርጾ ህዝቡን ወደ ሁከት ለማስገባት ጦርነት አውጇል » በማለት ወነጀሉ። • በሱዳን የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ትናንት ሰኞ በደቡብ ምስራቃዊዋ የሲንጃ ከተማ በፈጸመው የድሮን ጥቃት 27 ሰዎች ተገደሉ ። • በመንግስት የተቃዉሞ አመጽ እና ድጋፍ መሃል እየተናጠች በምትገኘው ኢራን የሟቾች ቁጥር 646 መድረሱ ተነገረ።
    Más Menos
    11 m
  • የጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
    Jan 12 2026
    የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) እና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አዲስ የሚገነባው የቢሾፍቱ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ግንባታ የአከባቢው ማህበረሰብ ላይ ስጋትን ደቅኗል አሉ፡፡ ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ሥደተኞችን የመርዳት የሞራል፣ የሰብአዊነትና የሕግ» ኃላፊነት እንዳለበት አዲሱ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር (UNHCR) የበላይ ኃላፊ አስታወቁ። ኢራን ለጦርነትና ለሰላማዊ ውይይት ለሁለቱም ተዘጋጅቻለሁ አለች።
    Más Menos
    12 m
  • የጥር 3 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
    Jan 11 2026
    • ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ወደ ጂቡቲ አቅንተው ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ዑመር ጊሌህ ጋር ተነጋገሩ ። • ቻይና ፣ሶማሊያ ሉአላዊነቷን ለማስጠበቅ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች። • የሱዳን ብሔራዊ ጦር መንግስታዊ መቀመጫ በስደት ላይ ከነበረበት ወደ መዲናዪቱ ካርቱም ተመለሰ። • አሜሪካ ተቃዋሚዎችን ወግና በኢራን ላይ ጥቃት የምትፈጽም ከሆነ እስራኤል እና የአሜሪካ ወታደሮች ዒላማዋ ሊሆኑ እንደሚችሉ አስጠነቀቀች ። • አሜሪካ ፍሎሪዳ ባስተናገደችው 46ኛው የአለም አገር አቋራጭ ውድድር ኢትዮጵያ በሁለተኛነት አጠናቀቀች ።
    Más Menos
    7 m