• የዓለም ዜና

  • De: DW
  • Podcast

የዓለም ዜና

De: DW
  • Resumen

  • ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።
    2025 DW
    Más Menos
Episodios
  • የዓለም ዜና ፤ ሚazeያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም ማክሰኞ
    May 6 2025
    አርስተ ዜና፤--የክርስቲያን ዴሞክራቶች ኅብረት ፓርቲ መሪ ፍሪድሬሽ ሜርስ አዲሱ የጀርመን መራኄ መንግሥት ሆኑ። ከሁለተኛዉ የዓለም ጦርነት ወዲህ 10ኛዉ የጀርመን ቻንስለር ሜርስ ቃለ-መሃላ ፈፅመዉ ሥልጣኑን በይፋ ተረክበዋል።--በአማራ ክልል ከመተማ ጎንደር ያለው መንገድ ከተዘጋ አንድ ወር በማስቆጠሩ በአካባቢው ነዋሪዎች የማህበራዊና ኢኮኒሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ጫና ማሳደሩን ነዋሪዎች ተናገሩ።--ለሃገራት የሚሰጠዉ ሰብዓዊ እርዳታ መቀነስ በዓለም አቀፍ ደረጃ እድገት እንዲቀዛቀዝ ምክንያት ሆኗል ሲል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ።
    Más Menos
    12 m
  • DW Amharic ሚያዝያ 27 ቀን 2017 የዓለም ዜና
    May 5 2025
    የእስራኤል ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ሳር ለሥራ ጉብኝት ኢትዮጵያ ገቡ። በአማራ ክልል ደሴ እና ወልድያ ከተሞች የአጭር ርቀት አሽከርካሪዎች ከዛሬ ጀምሮ የሥራ ማቆም አድማ አደረጉ። የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች በሱዳን በተፈጸመ የጅምላ ፍጅት ተባባሪ ሆናለች በሚል የሱዳን መንግሥት ያቀረበውን ክስ የተመ ፍርድ ቤት ውድቅ አደረገ። የኬንያው ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ በጫማ ተመቱ። የጀርመን ክርስቲያን ዴሞክራቶች ኅብረት ፣ ክርስቲያን ሶሻል ኅብረት እና ሶሻል ዴሞክራት ፓርቲ (SPD) ጥምር መንግሥት የመሠረቱበትን ሥምምነት ተፈራረሙ። እስራኤል ጋዛን ሙሉ በሙሉ ለመያዝ የሚያስችል ዕቅድ ማጽደቋን ባለሥልጣናት ተናገሩ።
    Más Menos
    12 m
  • የሚያዝያ 26 ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
    May 4 2025
    *የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ዛሬ እሁድ በፖርት ሱዳን ከተማ ላይ የድሮን ጥቃት መሰንዘሩን የሱዳን ብሔራዊ ጦር ቃል አቀባይ ተናገሩ። *የየመን ሁቲ አማጺያን በዓለም አቀፉ የቴል አቪቭ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ያነጣጠረ የሚሳኤል ጥቃት መሰንዘራቸውን ተከትሎ እስራኤል ከፍተኛ የአፀፋ እርምጃ እንደምትወስድ ገለፀች። *የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ምን ያህል የሀገሪቱን ህገ መንግሥት የማክበር ግዴታ እንዳለባቸው ርግጠኛ እንዳልሆኑ ተናገሩ። *ኢትዮጵያውያኑ ለሚ ብርሃኑ እና ብርቱካን ወልዴ በቼክ ሪፑብሊክ ዋና ከተማ ፕራግ ዛሬ የተካሄደውን የማራቶን ውድድር በየዘርፋቸው አሸነፉ
    Más Menos
    8 m
adbl_web_global_use_to_activate_webcro805_stickypopup

Lo que los oyentes dicen sobre የዓለም ዜና

Calificaciones medias de los clientes

Reseñas - Selecciona las pestañas a continuación para cambiar el origen de las reseñas.