Episodios

  • "ተግዳሮት ፊታችን ሲጋረጥ፣ መልካም ዕድልንም ይዞ እንደሚመጣ ማመን፤ ተስፋ አለመቁረጥና ራስን ለአዲስ ነገር ክፍት ማድረግ ያስፈልጋል" በኩረ ትጉኅን ኃይለልዑል ገብረሥላሴ
    Feb 12 2026
    በኩረ ትጉኅን ኃይለልዑል ገብረሥላሴ፤ ከውልደትና ዕድገት፣ የትምህርትና ሥራ፣ የተግዳሮትና ስኬት የሠፈራ ሕይወታቸውን የዳሰሱበትን የግለ ሕይወት ትረካ በምልሰታዊ ምልከታ ይቋጫሉ። የወደፊት ትልማቸውንም ያጋራሉ።
    Más Menos
    13 m
  • በኩረ ትጉኅን ኃይለልዑል ገብረሥላሴ፤ ትምህርት፣ ሥራና የአውስትራሊያ ክብር ሽልማት
    Feb 12 2026
    በኩረ ትጉኅን ኃይለልዑል ገብረሥላሴ፤ በሀገረ አውስትራሊያ ከመንፈሳዊ የአገልግሎት ተልዕኳቸው ጎን ለጎን ስላካሔዷቸው የትምህርትና የሥራ ዓለም ሕይወታቸው ነቅሰው ያወጋሉ።
    Más Menos
    22 m
  • በኩረ ትጉኅን ኃይለልዑል ገብረሥላሴ፤ ከነገሌ ቦረና እስከ አውስትራሊያ
    Feb 10 2026
    በኩረ ትጉኅን ኃይለልዑል ገብረሥላሴ፤ ከውልደት ቀዬአቸው ነገሌ ቦረና እስከ ሁለተኛ ሀገራቸው አውስትራሊያ የተጓዙበትን የመንፈሳዊና ዓለማዊ ግለ ሕይወት ታሪካቸውን ያጋራሉ።
    Más Menos
    21 m
  • ሀገራዊ ቃል ኪዳን "ባለቤቴን ለትዳር ስጠይቃት 'እኔ ሀገሬ ላይ ነው መኖር የምፈልገው፤የአንቺ ሃሳብ ምንድነው? ይህን ማወቅ አለብኝ አልኳት' ዳንኤል አለማር
    Aug 30 2025
    ዳንኤል አለማር፤ በቀዳሚው ክፍለ ዝግጅታችን የግለ ታሪክ ወጉ እንደምን በለጋ የወጣትነት ዘመኑ ከእነ ቤተሰቡ ለሀገረ ኬንያ የስደት ሕይወት እንደበቃና እንደተወጣው አውግቷል። በመቋጫው፤ የአውስትራሊ አዲስ የሕይወት ምዕራፍ ጅማሮውን፣ ተግዳሮቶችና መልካም ዕድሎችን አንስቶ ይናገራል።
    Más Menos
    23 m
  • "ለዛሬ መድረሻዬ ሆነኝ የምለው፤ በስደት ካምፕ የነበረኝና የሰንቅኩት ሕይወት ነው" ዳንኤል አለማር
    Aug 30 2025
    "የኃይለ ሥላሴ ቤተሰብ ነው እንዳትነኩት" - ዳንኤል አለማር፤ በግለ ታሪክ ወጉ ገና ለአካለ መጠን ሳይደርስ በለጋ ዕድሜው ከእናትና ወንድሞቹ ጋር እንደምን የትውልድ ሀገሩን ኢትዮጵያን ለቅቆ ለኬንያ የስደት ካምፕ እንደተዳረገና የኢትዮጵያ ስም እንደምን ከእሥር እንዳስለቀቀው ነቅሶ ያወጋል።
    Más Menos
    13 m
  • "ኢትዮጵያውያን መጥተው ድጋፋቸውን ቢቸሩኝ ደስ ይለኛል" ሶሊያና እርሴ
    Apr 3 2025
    አንፀባራቂ ኮከብ በመሆን ላይ ያለችው ሶሊያና እርሴ፤ ከትውልድ ከተማዋ ጎንደር፣ ከዕድገት ክፍለ ሀገሯ ትግራይ ተነስታ፤ እንደምን ትንፋሽን የሚያስውጥ፣ የልብ ትርታን ከፍና ዝቅ የሚያደርግ፣ ምትሃታዊ እንጂ ከቶውንም የመድረክ ዕውነታ የማይመስለው፤ ግና ሞገስን የተላበሰ አካላዊ መተጣጠፍ ኮንቶርሽን ተጠባቢ ለመሆን እንደበቃች ታወጋለች። ከኤፕሪል 3 እስከ ሜይ 11 በሜልበርን ከተማ Meat Market ከ Club Kabarett ጋር በመሆን ለሕዝብ ስለምታቀርበው ዝግጅቷ ታነሳለች። የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላትም በሥፍራው እንዲገኙ ትጋብዛለች።
    Más Menos
    9 m
  • "የትም ሀገር ብንሆን ኢትዮጵያን ከውስጣችን ማውጣት አይቻልም፤በአፍሪካ የመጀመሪያው በሆነው የሰርከስ ማዕከል ግንባታ ኢትዮጵያውያን ተሳታፊ ቢሆኑ ደስ ይለኛል"ሶስና ወጋየሁ
    Jan 29 2025
    የቀድሞዋ ኢትዮ - ሰርከስ ኮከብ አባልና የኢትዮ - ሰርከስ ኢንተርቴይንመንት ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሶስና ወጋየሁ፤ ከግለ ሕይወት ታሪካቸው ጋር አሰናስለው እንደምን ከሀገረ አውስትራሊያ ወደ ሀገር ቤት በመመለስ፤ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሚሆነውን የሰርከስ ማዕከል በእንጦጦ ፓርክ በመገንባት ላይ እንዳሉ ይናገራሉ።
    Más Menos
    22 m
  • ሶስና ወጋየሁ፤ ከአውስትራሊያ ጥገኝነት ጥየቃ ለክብር ሽልማት መብቃት
    Jan 21 2025
    የቀድሞዋ ኢትዮ - ሰርከስ ኮከብ አባልና የኢትዮ - ሰርከስ ኢንተርቴይንመንት ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሶስና ወጋየሁ፤ እንደምን በሀገረ አውስትራሊያ ከጥገኝነት ጥየቃ ለከፍተኛ የክብር ሽልማት እንደበቁ ያወጋሉ።
    Más Menos
    14 m